Skip to main content

Posts

Showing posts from September, 2022

አምባሰል ፥ ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም

  የአማራ ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ጣሂር መሃመድ በአንባሰል ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም ተገኝቶ  " አምባሰል ለገደል ፥ ምን? ያሽሟጥጡታል  ፈረስ ባያስጋልብ ፥ " ማር! " ይቆርጡበታል! " ይለናል።  ሲወርድ ሲዋረድ ከአባቶቹ ያገኘው ሥነ ቃል ነው። በነገራችን ላይ " ማር! " የሚለው ዝም ብሎ እንደ እንግዳ ደራሽ ፥ እንደ ውኃ ፈሳሽ ዝም ብሎ ለሥነ ቃል ማሳመርያ የገባ አይደለም። ጥንተ ነገሩ እንዲህ ነው።  አምባሰል በአማራ ክልል ኢትዮጵያ የሚገኝ ወረዳ ሲሆን በወረዳው ውስጥ የሚገኘው አምባ ወይም የግሸን ተራራ መታወቂያው ነው። አምባሰል የሚለው ቃል አምባ እና አሴል ከሚለው ሁለት ቃል የተገኘ ሲሆን አምባ ማለት ተራራ “አሴል” ማለት ደግሞ የአረበኛ ቃል ነው ትርጉሙም ማር ማለት ነው። " የማር ተራራ ! " ፥ “የማር መሬት” እንደ ማለት ነው።  በደቡብ ወሎ ዞን ውስጥ የሚገኘው አምባሰል ወረዳ በምዕራብ፦ በሺሎ ወንዝ ተንታ ፣ በሰሜን፦ ሰሜን ወሎ ዞን፣ በደቡብ ምስራቅ፦ ሚሌ ወንዝ ተሁለደሬ፣ በደቡብ፦ ኩታበር ያዋስነዋል። ከተማው ደግሞ ውጫሌ ይሰኛል። ከቀዳማዊው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ እስከ ቀዳማዊው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ኃይለ ሥላሴ ድረስ የአምባሰል አውራጃ ገዥ የቤተ አማራ (ወሎ) ግዛት አስተዳደር ጃንጥራር ይሰኝ ነበር። እቴጌ መነን አስፋው የአፄ ኃይለ ሥላሴ ባለቤት የአምባሰል ጃንጥራር አስፋው ልጅ ነበረች።

የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አራት የዩክሬይን ክልሎችን መቀላቀላቸውን አስታውቀዋል።እነሱም ሉሃንስክ፣ ዶኔትስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዝዝሂያ ናቸው።

 የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አራት የዩክሬይን ክልሎችን መቀላቀላቸውን አስታውቀዋል።እነሱም ሉሃንስክ፣ ዶኔትስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዝዝሂያ ናቸው።  ዩክሬን እና ምዕራባውያን ህዝበ ውሳኔው ህጋዊ አይደለም ሲሉ ውህደቱም ህገወጥ ሲሉ ቢያወግዙ  የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ዩክሬን በፍጥነት የኔቶ ወታደራዊ ህብረትን ለመቀላቀል በይፋ እንደ ሚጠይቁ ቢዝቱ  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የአራቱ ክልሎች መጠቃለል ምንም አይነት ህጋዊ እሴት የሌለው እና ሊወገዝ የሚገባው ነው። ቢሉም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የብሪታንያ አምባሳደር ባርባራ ዉድዋርድ “በዚህ ላይ ምንም መካከለኛ አቋም የለም” ሲሉ የሚስተር ጉተሬስን መግለጫ ቢያስተጋቡ  "ሩሲያ የጠቀለለችው ቦታ ከ90,000 ካሬ ኪሎ ሜትር በላይ ነው:: " ይህ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ትልቁ የግዳጅ ግዛት ነው።"

ዛሬ መስከረም 21 ፥ ዕለተ ቅዳሜ ፥ 2015 ዓ.ም አንባሰል ፥ ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም በሚሉዮን በሚቆጠሩ ሰዎች ደምቆ እየተከበረ ይገኛል።

 ዛሬ መስከረም 21 ፥ ዕለተ ቅዳሜ ፥ 2015 ዓ.ም አንባሰል ፥ ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም በሚሉዮን በሚቆጠሩ ሰዎች ደምቆ እየተከበረ ይገኛል።  ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም በአሁኑ ወሎ ክፍለ ሃገር፣ አምባሰል ወረዳ ፥ በግሸን ተራራ አናት ላይ የምትገኝ ቤ/ክርስቲያን ናት። የቤ/ክርስቲያኗ መግቢያ መንገድ አንድ ብቻ ነው። እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ቤተ ክርስቲያኗ በየዘመኑቱ የተለያየ ስያሜ አሏት። ከአጼ ድልናአድ ዘመን 866 ዓ.ም እስከ 11ኛው ክፍለ ዘመን በአሁኑ ስያሜ " ደብረ ከርቤ " በመባል ትታወቅ ነበር። በ11ኛው ክፍለ ዘመን አጼ ላሊበላ ከቋጥኝ ድንጋይ ፈልፍለው እግዚአብሔር አብ የተሰኘ ቤ/ክርስቲያን በዚሁ ቦታ ሲያሰሩ ደብረ እግዜአብሔር በሚል ስም ተጠራች። ብዙ ሳይቆይ ደግሞ ደብረ ነገስት ተባለች። በ1446 አጼ ዘርአ ያዕቆብ ግማደ መስቀሉን በዚህ ስፍራ ሲያመጡ ደብረ ነገስት መባሏ ቀርቶ ደብረ ከርቤ ተባለች። በዚህ ጊዜ የነበረው የቤ/ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ " መምህረ እስራኤል ዘ ደብረ ከርቤ! " ይባል ነበር። አጼ ዘርዓ ያዕቆብ ግማደ መስቀሉን ይዘው እየገሰገስገሱ ስለመጡ በግዕዙ "ገሰ" ወይም በአማርኛው "ገሰገሰ" የሚለው ቃል ለቦታው ስያሜ ሆነ። በዘመናት ሂደት ገስ ወደ ግሸን የሚለው ስያሜ ተዛወረ። አካባቢው በዚህ ስም ታወቀ።

" ኢሬቻን ሁሉን የኦሮሞ ዋና ዋና ጎሳዎች ሜጫ እና ቱለማ፣ ሰቦ ጎና፣ ሲኮ ሜንዶ፣ ኢቱ ሁንበናን ያሰባሰበ የምስጋና በዓል ነው።"

 የኦሮሞ ተወላጆች የባህል ልብስ ለብሰው "ኢሬቻ" የተሰኘውን የምስጋና በዓል ለማክበር አዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ ፓርክ ዛሬ መስከረም 21 ፥ ዕለተ ቅዳሜ ፥ 2015 ዓ.ም ተገኝተዋል። ነገ እሁድ ደግሞ በደቡብ ማእከላዊ ቡሾፍቱ ከተማ በሚገኘው ሆራ ሃርሰዴ ሃይቅ ያከብራል። ፌስቲቫሉ በቢሾፍቱ ከተማ ለዘመናት ሲከበር፣ በ2019 ከ150 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓላቱ ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ እንደ ተመለሰ ተወላጆች ያወራሉ። በቡድን የተሰባሰቡ ሰዎች በኦሮምኛ እየዘፈኑ እና እየጨፈሩ ጥቁር፣ ቀይ እና ነጭ ባለ ሶስት ቀለም ባህላዊ ልብስ ለብሰው ወደ ሀይቁ ይጎርፋሉ። የጋዳ ሽማግሌዎች " ዋቃ! " ተብሎ ለሚጠራው የኦሮሞ አምላክ በሃይቁ ላይ ለምለም ሳር ክምር በመንከር በጭንቅላታቸው እና በአካላቸው ላይ ውሃ በመርጨት እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ። " ኢሬቻን ሁሉን የኦሮሞ ዋና ዋና ጎሳዎች ሜጫ እና ቱለማ፣ ሰቦ ጎና፣ ሲኮ ሜንዶ፣ ኢቱ ሁንበናን ያሰባሰበ የምስጋና በዓል ነው።" የሀገር ሽማግሌዎች " ኢሬቻ የመራባት እና የሰላም በዓል ነው። ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ሰላም እንጸልያለን። " ይላሉ።

ስለ ኢሬቻ ትውስታ

ኢሬቻ የዝናብ ወቅት አብቅቶ የመኸር ወቅት መጀመሩን ያመለክታል። ከአዲስ አበባ በስተደቡብ ምስራቅ 50 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው በቢሾፍቱ ከተማ ሆራ አርሰዲ እና በአዲስ አበባ ሆራ ፊንፊኔ በድምቀት ይከበራል።  እ.ኤ.አ. በ 2016 በቢሾፍቱ ከተማ በኢሬቻ በዓል የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ እና ሽጉጥ በመጠቀማቸው የበርካታ ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ችሏል። የተወሰኑት ሰዎች ደግሞ በአቅራቢያው በሚገኝ ሃይቅ ውስጥ ሰጥመው ሙተዋል።  እ.ኤ.አ. በ 2017 በቀጣዩ ዓመት ኢሬቻ ወደ ፀረ-መንግስት ተቃውሞ ተቀየረ። ጠቅላይ ሚኒስተር ዐብይን በ2018 ወደ ስልጣን ያመጣው የእንቅስቃሴ አካልም ሆነ። ዛሬ ኢሬቻ በኦሮሞ ባህል መሪዎች እየተመራ በመሃል አዲስ አበባ በውሃ ገንዳዎች ላይ አበባ እየነከረ በራሱ ላይ በመርጨት የምስጋና እና የመታደስ ምልክት የሚያሳይ ትልቅ በዓል ሆነ።