ከቋራ እስከ አርማጭሆ ወልቃይት ጠገዴ ሁመራ
• ከተለያዩ ክፍለ-ሀገሮች በመነሳት ወደ ሰሊጥ አጨዳ ለመሄድ አማራጭ መንገዶች!!!!
•
• ከጎንደር ~ሳንጃ ~ ሶሮቃ ~እርጎዬ ~በመጓዝ አብርሃጅራ ላይ በመውረድ ወደ አብደራፊና ኮርሁመር ወደ ማርዘነብና ስናር እንዲሁም ወደ ቀጭኔና ጎደቤ የኢንቨስትመንት ቀጠና መድረስ ይቻላል
•
• ከጎንደር ~ሳንጃ ~አሸሬ ላይ በመዉረድ ወደ ደለሳና ወደ ጋብላ የእርሻ ኢንቨስትመንት ቦታዎች መግባት ይቻላል፡፡
•
• ከጎንደር ዳንሻ በመዉረድ ~ማይደሊ ድቭዥን እና እብናትን ጨምሮ የዳንሻን ከጎንደር ~ሁመራ በመዉረድ ወፍ አርግፍ የቃብትያ~ አካባቢን ማግኘት ይቻላል።
•
• ከጎንደር በዕከር በመዉረድ የባህረ ሰላምን ጭምሮ አካባቢውን ማግኘት ይቻላል።
• ከጎንደር ሁመራ በመዉረድ የማይካድራ እና በረከት አካባቢን ማግኘት ይቻላል።
• ከጎንደር ሳንጃ ሰጋሎ ቅራቅር በመዉረድ የአዴት የጠገዴን አካባቢን ማግኘት ይቻላል።
• ሳንጃ ~ሶሮቃ~እርጎዬ ~ኪሻ ላይ በመዉረድ ወደ ጠገዴ የእርሻ ቦታዎችና ወደ መሃርሽ እንዲሁም ወደ ዘመነ መሪቅ እና ድርማጋ መግባት ይቻላል።
• ከጎንደር አዘዞ~ቆላድባ ደልጊ ~ሻውራ ~በሙር ላይ በመውረድ ወደ አባይዳር የኢንቨስትመንት ቀጠና መግባት ይቻላል።
• ከ ጎንደር አዘዞ ~ ቆላድባ~ ደልጊ~ ሻውራ~ በሙር ገለጉ~ ዱባባ ላይ በመውረድ ወደ ምርት ገለጉ እና ነብሰ ገበያ የ ኢንቨስትመንት ቀጠናወች መግባት ይቻላል።
• ከ ጎንደር አዘዞ ቆላድባ~ ደልጊ ሻውራ ~በሙር ገለጉ~ ዱባባ ~ሽንፍ ላይ በመውረድ ወደ ነብሰ ገበያ እና ቁጥር 4 የ ኢንቨስትመንት ቀጠናወች መግባት ይቻላል።
• ከ ጎንደር~ ቆላድባ ~ደልጊ ~ሻውራ ~በሙር ገለጉ~ ዱባባ~ ሽንፍ በኩል ወደ ~ገንድ ውሃ መስመር
• በጎጃም በኩል ደግሞ
• ከባህርዳር - ጭምባ - ቁንዝላ - ሻሁራ - ገለጎ - ወደ ቋራ - መተማና ሌሎች መግባት ይቻላል።
• ከዱርቤቴ - ይስማላ - ሊበን - ቁንዝላ - ሻሁራ - ገለጎ - (ወደ ቋራ -መተማና ሌሎች) መግባት ይቻላል።
• በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው ከቋራ እስከ ሁመራ ያለው ምድር እጅግ ውብ፣ ለአይን የሚያሳሳ፣ ሰፋፊ የእርሻ ቦታ ያለው
• የነጭ ወርቆች ምድር (ሰሊጥ ፤ አኩሪ አተር ፤ ሱፍ ፤ ጥጥ፤ ማሽላ ፤ ሩዝ ፤ ማሾ የሚመረቱበት)
• አመቱን ሙሉ የሚፈሱ ትልልቅ ወንዞች ያሉበት በመሆኑ በቂ የውሃ ሀብት ያለው
• አስተማማኝ የዝናብ መጠን ያለው
• ምቹ ስነ-ምህዳር (ለሰብል ፤ ለእንስሳት ፤ ለመስኖ ፤ ለደን ልማት እጅግ የተመቼ)
• ለጥ ያለ፣ ዳርቻው ከሰማይ ጋር የተያያዘ የሚመስል
• ለም መሬት ያለው ድንቅ ምድር ነው፡፡
• ምዕራብ ጎንደር ብቻ ከ516ሺህ ሄክታር በላይ መሬት
• ለሰብል ልማት ምቹ ሲሆን በ2014/15 የምርት ዘመን ከ493ሺህ ሄ/ር በላይ መሬት በልዩ ልዩ ሰብሎች የተሸፈነ መሆኑን ከዞኑ ግብርና መምሪያ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡
• አኩሪ አተር ብቻ ከ127ሺህ ሄ/ር በላይ መሬት ተዘርቷል፡፡ ካለው ጠቅላላ መሬት ውስጥ ከ300ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ መልማት የሚችል ነው፡፡
• ከቋራ እስከ ሁመራ ያለው ድንቅ ምድር በአግባቡ በዘመናዊ ግብርና ስርዓት ቢለማ ሀገርን በእጅጉ መቀየር የሚችል፣ በሀገሪቱ ግብርና ክፍለ ኢኮኖሚ ላይ ታዕምር መፍጠር የሚችል አጓጊ ቀጠና ነው፡፡
• አካባቢው ከጎረቤት ሀገር ሱዳን ጋር በምዕራብ አቅጣጫ ሙሉ ለሙሉ የሚዋሰን በመሆኑ በተደጋጋሚ ለጸጥታ ስጋት ተጋላጭ ቢሆንም በጭንቅ ጊዜ ተኳሽ በሰላም ጊዜ አራሽ፣ በአንድ እጁ ትራክተር በሌላ እጁ ጠመንጃውን ይዞ የልማት ስራውን የሚያሳልጥ ጀግና ማህበረሰብ ያለበት አስገራሚ ምድር ነው!!

Comments
Post a Comment