ይሄ የጁ-ወልዲያ ያበቀለው ጀግናው አርበኛ የወሎው ፋኖ ሞገስ ከበደ ነው!--------
የጀግና ተግባሩ እንጂ አፉ አይናገርም። ሞገስ ከበደ የወልዲያ ከተማ፣ ጊራና፣ የራያ እና መሃል አምባ ልጆችን ይዞ በትናንትናው የጎብየ ግንባር ትግል በታሪክ ከፍ ብሎ የሚነገር፣ ልብን የሚያሞቅ፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮችን በግርምት አፍ ያስያዘ ጀብድ ፈጽሟል።
"ሞገስ ከዚህ በላይ ማለፍ በቀጣይ ጦርነት እንዳንሳተፍ የሚያደርግ አደጋ ላይ ይጥለናል" ብየ እጁን ያዝኩት ይላል ጠባቂው አህመድ መሐመድ!
ቀኝ እጄን ቀምቶ፣ ተተኳሽ የጨረሰ ክላሹን አዝሎ፣ "ይልቁን ራቅ ብለህ መሬት ያዝና እራስህን እየጠበቅክ ሽፋን ስጠኝ" ብሎ ከጎኑ የታጠቀውን ፈንጅ ነቅሎ ወደ እሳቱ መሃል ገባ። የታዘዝኩትን አደረግኩ ይላል ጓዱና ጠባቂው። ቀኑ ለጠላት የሞትና ውርደት ነበር፥ ሞገስ ከበደ እና ልጆቹ ለጠላት የማይቀመሱ ሆነው ዋሉ።
የወልዲያ፣ ጊራና እና መሃል አንባዎቹ ወጣቶች ገድል ለታሪክ ይቀመጥ። በዚህ ፍልሚያ ከማንም በላይ በራያ ግንባር ላይ ተቆጥተው የዋሉ፣ ለራያ ህዝብ ነፃነትና የልብ ኩራት የተዋደቁ እነሱ ነበሩ። ነብሱን በጨርቅ ቋጥሮ አሻግሮ ለሚመለከታቸው አስመሳይ የወንዜ ልጅ ሁሉ ትምህርት አስተላልፈዋል። ብቸኛው ምርጫችን አንድ መሆን፣ ለአንድ አላማ መታገልና መሞት ድልን እንደሚያቀዳጅ አሳይተዋል። ህወኃትን የመሰለ ጉንዳን ሃይል በመለያየትና በማስመሰል ማሸነፍ እምደማይቻልም አሳይተዋል።
እነዚህ ጀግኖች ሌላው ቀርቶ እጃቸው ውስጥ የገቡትን ምርኮኞች በብስጭትና እልክ ከማንገላታት ተቆጥበው ፥
"እንዲህ እንዲያልቁ ምክንያት የሆናቸውን እብደት ጠይቋቸው" ብለው ለአለቃቸው አስረክበዋል፥ ልዕለ ስብዕናና ጀግንነት ማለት እንደዛ ነው።
የራያ ወርቄው ቡቃያ መሐመድ ሰኢድ ሱሩር የአለቃውን ሞገስ ከበደን ቁጣ፣ ልመናና ተግሳጽ በእልክና ጀብድ ተላልፎ በክብር ወድቋል። "እነዚህ የራያ ታዳጊ የወርቄ ወጣቶች ተኩስ ውስጥ ሲገቡ ሰውነታቸው ይሞቃል፣ ባሩድን እንደ ጅራፍ ግርፊያ ቡታ የመቁጠር ጀብድ አለባቸው" ይላል አለቃቸው።
የመሀል አንባው ጀግና ደምሌ ፈንታው፣ የመርሳው ነብር ሞላ ከበደ እና የእዜቱ ታደሰ ጋሻዉ 24 ሰዓት ተዋግተዋል። ሁለቱ ጀግኖች በትግል ላይ የተሰው ሲሆን ደምሌ ፈንታው ግዳጁን በተሳካ ሁኔታ አሳክቶ ሲመለስ ከርቀት በተተኮሰ የጠላት ኢላማ በክብር ወድቋል። የሌሎቹን አናብስት ግዳይ ሳይጨምር ደምሌና ጓደኛው በአንድ ዙር ብቻ ከአስር በላይ ከባድ የሆኑ የጠላት ሃይል ተኳሾችን አሰናብተዋል። ክብር ለመሃል አምባው አርበኛ ፋኖ ደምሌ እና ጓዶቹ ይሁን!!
-------
ወራሪው ሃይል ሶስት ዙር በገባበት በዚህ ግንባር አንድም ጊዜ ሙት ሳያነሳ ለመሸሽ ተገዷል። የሚደንቀው ነገር ጠላት ትጥቁን ቀርቶ ያስቀመጠውን መገናኛ ሬድዮ ለማንሳት ፋታ ሳያገኝ ሲገረፍና ሲረግፍ ውሏል።
"ተልዕኮህን በተሳካ ሁኔታ ተወጥተሃል፣ ቦታውን ለቀህ ውጣ ወይም ተጨማሪ ቦታ ልስጠህ? ሲል አዛዥ ክረኔሉ ሞገስ ከበደን ጠየቀው።
"ጠላት ይሄንን ቦታ ለቆ ሳይወጣ አልወጣም፣ ቦታ ስጠኝ" አለ ጀግናው! ባደረበት ግንባር እንደገና ዋለበት። ከሀምሳ በላይ የነብስ ወከፍና የቡድን መሳሪያዎችን ማርኮ በክብርና ሞገስ ምሽጉን ለሀገር መከላከያ ሰራዊት አስረክቦ ወታደሮቹን አስከትሎ እየተንጎባለለ ወጣ።

Comments
Post a Comment