Skip to main content

የአማራ ወጣቶች ማህበር በሸዋ መስከረም 2015 ዓ.ም አንደኛ መደበኛ ጉባኤ አድርጓል።

 


የአማራ ወጣቶች ማህበር በሸዋ!!


የአማራ ወጣቶች ማህበር በሸዋ ባጣናቸው የህዝብ ልጅ ማዲንጎ አፈወርቅ፣ለምስራቅ አማራ ፋኖ አባል አሸናፊ አለሙ እና በወለጋ በሞቱት ንፁሃን እናቶች፣አባቶች፣እህቶች ወንድሞች ህፃናት የደረሰብንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን የሚፈሱት እያንዳንዱ የደም ጠብታ የሚወርዱት የመከራ ናዳ ህዝባችንን ትንሳኤ ለማምጣት የሚያፋጥኑ ናቸው።

በብዙ መከራ ውስጥ ብንሆንም የአማራ ህዝብ የሚድንበትን እና ይህን የመከራ ችግር የሚያልፍበትን መንገድ ይቀይሳል። ማህበራችንም በነዚህ እና መሰል ችግሮች ውስጥ ሆኖ ለመላው የአማራ ህዝብ እና ለማህበራችን ደጋፊዎች አባላት ማህበሩ መስከረም 2015ዓ.ም አንደኛ መደበኛ ጉባኤ አድርጓል።በዚህም ማህበሩ ያሉበትን ክፍተቶች አሟልቶ ስብሰባውን አድርጓል።

በዚህም ጉባኤ ማህበሩ ኮሚቴውን በማጠናከር ስብሰባውን ጀምሯል። ስብሰባውን ሲጀምር ከታች ያሉትን ኮሚቴዎች ሹመት በማፅደቅ ጀምሯል፦
• ሰብሳቢ                       
• ፀሃፊ                          
• ህዝብ ግንኙነት              
• ጥናት አና  እስትራቴጂ       
• አካውንታት                         
• ሂሳብ ሹም                        
• ግዥና ሃብት አሰባሳቢ           
• ክልላዊና ሃገራዊ የህዝብ ትስስር  
• ባህልና ቅርስ ኦፊሰር
• ቅሬታ ሰሚ ኦፊሰር
•  ሚዲያና ኮሚኒኬሽን
•  አዛውንቶች ሴቶች
• ኪነጥበብ ስራወች
• ኪነጥበብ ስራወች
• ታሪክና ጥናት ሃላፊ
• አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ
• የህግ አማካሪ

በቀጣይ የሚሰራቸውን ስራዎች በእቅድ አስቀምጦ።በክልላችን ያሉትን ችግሮች በመልቀም ከክልላችን ውጪ ያሉትንም የህዝቦቻችንን ስቃይ በጠነከረ የህዝብ ትግል በጋራ ያመጣነውን የትህነግ ለውጥ አሁን በለቅሶ ሳይሆን በጠንካራ የህዝብ ትግል አዲስ ለውጥ ለማምጣት በጋራ ቃል ገብቶ ስብሰባውን አጠናቋል። ህዝባችንም እየታዩ ያሉት አማራን የማጥፋት ስራ ለማክሸፍ እራሱን እንዲያዘጋጅ ጥሪ አቅርቧል።
  በመጨረሻም የአማራ የፀጥታ ሀይል ማለትም ፖሊስ፣ልዩሀይል አርማ ብተና በተረኝነት በትር እየቆሰለ ካለው የህዝብ ልጅ ጎን ሆኖ ከፋኖ ወንድሞቹ ጋር በጋራ በመቆም እራሱን እንዲጠብቅ ለእውነት ዘብ እንዲሆን በማለት ጉባኤውን ቋጭቷል።
                                                             

Comments

Popular posts from this blog

አርሲ እና የአርሲ ሴቶች ባህል

  በዳዊት ፀሐይ አርሲ በማዕከላዊ የኢትዮጵያ ክፍል በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚገኝ ክልል ነው።  በዋናነት በአካባቢው በሚኖሩ በአርሲ ሰዎች ስም ተሰይሟል።  የአርሲ ዞን ወደ 17,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ከ3 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይኖራል።  ክልሉ በተለያዩ መልክዓ ምድሮች የሚታወቅ ሲሆን ይህም ደጋ፣ ቆላማ እና ደኖችን ያጠቃልላል።  በተጨማሪም የላንጋኖ ሀይቅ እና የዝዋይ ሀይቅን ጨምሮ የበርካታ ወንዞች እና ሀይቆች መኖሪያ ነው።  በአርሲ ያሉ አብዛኛው ሕዝብ ዋናው የገቢ ምንጭ ግብርና ነው።  ክልሉ ቡና፣ ሻይ፣ በቆሎ፣ ስንዴ እና ሌሎች ሰብሎችን በማምረት ይታወቃል።  የእንስሳት እርባታ የኢኮኖሚው አስፈላጊው አካል ነው። አርሲ ካሏት ባህላዊ ቅርሶቿ በተጨማሪ የበርካታ ታሪካዊ ቦታዎች ባለቤትም ናት።  ከእነዚህም መካከል በ13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተጀመረው አዳዲ ማርያም ውቅር ቤተ ክርስቲያን እና የሶፍ ኦማር ዋሻ ( ከአፍሪካ ትልቁ የዋሻ ስርዓት አንዱ ነው። ) ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ናቸው፠ በአጠቃላይ አርሲ ልዩ የሆነ ባህልና ታሪክ ያላት በመልክአ ምድርና በተፈጥሮ ሀብት በእጅጉ የበለጸገች  ክልል ናት። በአርሲ ባህል ሴቶች ትልቅ ሚና አላቸው።  ቤተሰብን የማስተዳደር፣ ልጆችን የማሳደግ እና በቤተሰቡ ገቢ ላይ በእርሻ ወይም በትንንሽ ንግዶች የበኩላቸውን አስተዋፅኦ የማድረግ ሃላፊነት አለባቸው።  ሴቶች በማህበረሰብ ውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች በተለይም ከማህበራዊ ደህንነት እና ልማት ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ጉልህ ሚና ይጫወታሉ። በአለባበስ ረገድ የአርሲ ሴቶች በተለምዶ ሸማ የሚባል የባህል ልብስ ይለብሳሉ። ከጥጥ የተሰራ እና በቀለማት ያሸበረቀ ነው።...

ነጻ የወጣችውን ራያ ቆቦን ወገን ለመቼ ነው በሚል ስፍራው ጋ ደርሰን የህዝቡን አኗኗር እና ስነ ልቦና አይተናል።

   ከብዙ በጥቂቱ ፥ ከሙሉ በክፍሉ ነጻ የወጣችውን ራያ ቆቦን ወገን ለመቼ ነው በሚል ስፍራው ጋ ደርሰን የህዝቡን አኗኗር እና ስነ ልቦና አይተናል።ከሁለት ዓመት በውኋላ ተቋርጦ የነበረው መብራት ስለ መጣ ከተማው በተኩስ ሲናጥ አድሯል።   ቆቦ በሰሜን ኢትዮጵያ ÷ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን የምትገኝ ከተማ ናት  ቆቦ ከባህር ጠለል በላይ 1468 ሜትር ከፍታ ላይ ትገኛለች።   ቆቦ በምዕራብ በኩል በኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች እና በምስራቅ በአፋር የእሳተ ጎሞራ ጭንቀት ያዋስናታል።  በታሪክ ራያ አንጎት ተብላ ትጠራ ነበር። ራያ ቆቦ የአማራ ህዝብ ነው። አንጎት በአማራ ክልል ወልድያ አቅራቢያ ከሀብሩ ወረዳ በደቡብ በኩል እስከ ማይጨው ራያ አዘቦ የሚደርስ ሜዳ ነው።  ይህ ስፍራ ከኢፋት ሱልጣኔት (13ኛው ክፍለ ዘመን) ጊዜ ጀምሮ በክርስቲያን ደጋማውያን እና በምስራቅ በመጡ ሙስሊሞች መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ውስጥ ነበር።  አብዛኛው ቀደምት ግጭት የተካሄደው በደቡብ በኩል በምስራቅ ድንበር ነበር። አሁን ሸዋ ነው።   ነገር ግን በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አንጎት አሁን ራያ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በአዳል ጀነራል አህመድ ኢብኑ ኢብራሂም አል-ጋዚ ጦር እና በኢትዮጵያው አጼ ልብነ ድንግል ከፍተኛ ግጭት ጊዜ የውጊያ መዐከል ነበር። ይህ አስነዋሪ የግጭት ዘመን የኢትዮጵያና የአዳል ጦርነት በመባል ይታወቅ ነበር።  አጼ ልብነ ድንግል የካቲት 10 ቀን 1541 ምጽዋ ወደብ ከደረሱት ፖርቹጋሎች እርዳታ ጠየቁ። በሚያዚያ ወር 1542 የሁለቱ ሠራዊት ከአሸንጌ  ሃይቅ በስተሰሜን በኮረም አካባቢ ተገናኙ። ይህም ውጊያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዘመናዊ ጦር መ...

የወላይታ ንጉስ ካኦ ጦና

በዳዊት ፀሐይ  ካኦ ጦና በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ የገዛ የወላይታ ንጉስ ነበር።  ወላይታ በደቡብ ኢትዮጵያ ደጋማ አካባቢዎች የሚገኝ ክልል ነው።  የራሱ የሆነ ቋንቋ እና ባህል ያለው የወላይታ ህዝብ መኖሪያ ነው።  ክልሉ በቡና ምርት የሚታወቅ ሲሆን በተፈጥሮ ውበቱ የቱሪስት መዳረሻም ነው።  እናም ካኦ ጦና በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ዘመን የኢትዮጵያን ግዛት መስፋፋት በመቃወም ይታወቃሉ።  ካኦ ቶና ህዝቡን እየመራ ከኢትዮጵያ ጦር ጋር ተከታታይ ጦርነት ቢያደርግም በመጨረሻ ግን ተሸንፎ እጅ ለመስጠት ተገደደ።  በስደት ወደ አዲስ አበባ ተወስዶ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ ኖረ።  ካኦ ቶና ቢሸነፍም በወላይታ ህዝብ ዘንድ እንደ ጀግና ሲታወስ ቆይቷል።  ትሩፋቱ በወላይታ አፈ ታሪክ እና ዘፈኖች የተከበረ ሲሆን ታሪኩ አሁንም ጭቆናን እና ኢፍትሃዊነትን ለመቃወም ይውላል። ስለ ጦርነቱ ማለትም ስለ ካኦ ጦና እና ዳግማዊ አጼ ምኒልክ መካከል ስለተደረጉ ጦርነቶች ዝርዝር መረጃ ማግኘት ይቻላል።  ሆኖም ካኦ ጦና ህዝባቸውን በመምራት በኢትዮጵያ ሰራዊት ላይ ተከታታይ የሽምቅ አይነት ጥቃቶችን ማለትም እንደ ማሸማቀቅ እና መምታት የመሳሰሉ ስልቶችን ሲጠቀሙ እንደነበር ታሪክ ያወሳል። ዳግማዊ አፄ ምኒልክም አመፁን ለመደምሰስ ብዙ ጦር ልከው ነበር።  ጦርነቱ ለብዙ አመታት የዘለቀ ሲሆን ሁለቱም ወገኖች ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶባቸዋል።  በመጨረሻም ካኦ ጦና ተሸንፎ እጅ ለመስጠት ተገዷል።  በስደት ወደ አዲስ አበባ ተወስዶም እስከ እለተ ሞቱ ድረስ ኖሯል። ፊታውራሪ ደስታ ፍስሐ የካኦ ጦና ልጅ